Tuesday, July 8, 2014

የእንግሊዝ ጠበቆች የውጪ ጉዳይ ቢሮውን ውጥረት ውስጥ ከተውታል።


Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)
የየመን ፕረዚዳንት እና የደህንነት ሃላፊው አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አሳልፈው ለመስጠት ከደብረጺሆን እጅ አንድ ሚሊዮን ዶላር እንደተቀበሉ አውቃለሁ ያለ አንድ ግለሰብ ለካምብሪጅ የጠበቆች ቡድን ጥቆማ ከሰጠ በኋላ ጠበቆቹ የእንግሊዝ ውጪ ጉዳይ ቢሮን አጣብቂኝ ውስጥ መክተታቸው ታወቀ።
ጉዳዩን በማስርጃ አስደግፎ የያዘው የ እንግሊዝ ጠበቆች ቡድን የየመን ፕረዚዳንት በሃገሪት ከሚካሄዱ የስለላ እና የደህንነት ጉዳዮች ጋር ቀጥተኛ የሆን ግንኙነት ያላቸው ሲሆን የአቶ አንዳርጋቸውን ጉድዳ ለመጨረስ የየመን ፕሬዚዳንት እና የደህንነት ሹሙ ከሌሎች ባለስልጣናቶች እውቅና ውጪ እንዲሁም ከየመን ውጪ ጉዳይ እውቅና ውጪ ይአንድ ሚሊዮን ዶላር የጉቦ ስምምነት በማድረግ አቶ አንዳርጋቸውን አሳልፈው ለመስትታቸው ማስረጃዎች በበቂ ሁኔታ ተይዘዋል።
እንዲሁም በየመን መንግስት ስም የትምባሆ ፋብሪካውን ደብረጺሆን በፊርማው አጽድቆ የሰጠ ሲሆን ይህ ከትንባሆ ፋብሪካ የሚገኘው ጥቅም ለፕሬዚዳንቱ እና ለደህንነት ሹሙ በየመን መንግስት ስም እንደሚሰጣቸው ተጠቁሟል፡፤
ምንድነው በኛው ጉዳይ ዝግ ስብሰባ ? … የአንዳርጋቸውን ቤተሰቦች መጥራት ለምን አስፈለገ?
ወያኔ ሌላ ዙር ቁማር ሊጀምር ነው ።
አዲስ አበባ አከባቢ ውጥረቶች በወያኔ ቢሮዎች እና በእንግሊዝ ዲፕሎማቶች አከባቢ ሰፍኗል። የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ቢሮ ባለስልጣናት እና የጠበቆች ቡድን በለንዶን ገለልተኛ የሆነ ስብሰባ አካሄዷል። የስብሰባውን ጉዳይ እናሳውቃቹሃለን ቢሉም እስካሁን ወደ ዝርዝር ጉዳዩ አልገቡም ፡፤ ሁኔታውን መዋሸት ስለማይችሉ እና እኛ መስማት የሚገባንን እንዳንሰማ ስላደረጉ ረዥም ሰአት ቢጠበቁም ስብሰባቸው ሊያልቅ አልቻለም … ብትከፍሉንም አንገለውም የሚለው ወያኔ ሌላ ዙር ቁማር ሊጀምር ነው ።
በተከታታይ በሎንዶን የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ቤተሰቦች በመጥራት ነገሩ ምነው yeጤና አይደለም ወይ እስኪያሰኝ ድረስ ሰአቱ ለመሻማት የሚያቅቱ ዝግ ንግግሮች ተደርገዋል። እነዚህን ቤተሰቦች የእንግሊዝ ዲፕሎማቶችም ሲጠሩ ሲመልሱ እስከመቼ ? ጉዳዩን በተመለከተ መረጃዎች ይቀጥላሉ ።

No comments: