Sunday, August 31, 2014

ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ያወጣው መመርያ ደንብ የጣሰ ነው የሚል ተቃውሞ ገጠመው

 | 


‹‹መመርያው የወጣው ክልሎች ተገቢውን ዕርምትና ጥበቃ ሊያደርጉ ስለማይችሉ ነው››
የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር
የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የሕግ ታራሚዎች ዝውውርን በሚመለከት ያወጣውና ከሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ተግባራዊ መደረጉ የተገለጸው የአፈጻጸም መመርያ ቁጥር 2/2006 ተቃውሞ ገጠመው፡፡

ተግባራዊ መደረግ የጀመረውን የማረሚያ ቤቱን የአፈጻጸም መመርያ የተቃወሙት፣ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች የሚገኙ ታራሚዎች ናቸው፡፡ ታራሚዎች በተለይ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የሕግ ታራሚዎችን በሚመለከት በአንቀጽ 21 (2) ሥር ባሰፈራቸው ድንጋጌዎች፣ በጥበቃ ሥር ያሉና በፍርድ የታሰሩ ሰዎች ከትዳር ጓደኞቻቸው፣ ከቅርብ ዘመዶቻቸው፣ ከሃይማኖት አባቶቻቸው፣ ከሐኪሞቻቸውና ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር የመገናኘትና እንዲጎበኟቸው ዕድል የማግኘት መብት እንዳላቸው ስለተደነገገ ደንብ መውጣቱን አስታውቀዋል፡፡ 
የሕገ መንግሥቱን የመብት ድንጋጌ ተከትሎ የሚኒስትሮች ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 138/99 አንቀጽ 19 ላይ የሕግ ታራሚዎችን የዝውውር ጥያቄ በሚመለከት እንደገለጸው፣ ማንኛውም ታራሚ የመጨረሻ ውሳኔ ተሰጥቶት በሌላ ክስ የማይፈለግ ከሆነ፣ ቤተሰቦቹ በሚኖሩበት አካባቢ ወደሚገኝ ማረሚያ ቤት እንዲዛወር ካመለከተ፣ ሊፈቀድለት እንደሚችልና ቤተሰቦቹም እንዲያውቁ እንደሚደረግ የተደነገገውን ደንብ መመርያው እንደሚጥስና ታራሚዎቹንም መብት እንደሚያሳጣ አስረድተዋል፡፡
መመርያ ደንብን ሊጥስ ወይም ሊያርም እንደማይችል የሚናገሩት ታራሚዎቹ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያወጣውን ደንብ ማረሚያ ቤቱ ምንም ሳይሸራረፍ ተፈጻሚ ማድረግ ሲገባው፣ አስተዳደሩ መመርያ እያወጣ መሠረታዊ መርሆዎችን መጣስ እንደማይችልና ተገቢም አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡
ማረሚያ ቤቱ ተግባራዊ ባደረገው ደንብ የሚጥስ የአፈጻጸም መመርያው ‹‹የሚኒስትሮች ምክር ቤት በደንብ ቁጥር 138/1999 አንቀጽ 19 ስለታራሚዎች ዝውውር የተደነገገ ቢሆንም›› ካለ በኋላ፣ ዝውውር የማይፈቀድባቸውን የወንጀል ዓይነቶች በዝርዝር ማስቀመጡን ታራሚዎቹ ተናግረዋል፡፡ በሰው ዘር ማጥፋት ወንጀል፣ በሽብርተኝነት፣ በሃይማኖት አክራሪነት፣ በአገር ክህደት፣ የአገሪቱን ሚስጥር አሳልፎ መስጠት፣ በከባድ ውንብድና፣ በጦር መሣሪያ ንግድ፣ በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር፣ በሙስና፣ ገንዘብ ማሳተምና ዝውውር፣ በሴቶች፣ በሕፃናትና በአካል ጉዳተኞች ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎችና ሌሎች በርካታ የወንጀል ዓይነቶችን አስተዳደሩ በመመርያው በመዘርዘር፣ በእነዚህ ወንጀሎች የተፈረደባቸው ታራሚዎች ከፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ወደ ክልሎች ማረሚያ ቤቶች መዘዋወር እንደማይችሉ ማስታወቁን ታራሚዎቹ ጠቁመዋል፡፡ አስተዳደሩ የወንጀል ዓይነቶቹ አዲስና ውስብስብ እንደሆኑ የገለጸ ቢሆንም ለዘመናት የነበሩና አዲስ አለመሆናቸውን ገልጸው፣ በአሁኑ ጊዜ ለዚያውም ደንብ ጥሶ ለመከልከል የፈለገበት መንገድ አሳማኝ አለመሆኑን ተቃውመዋል፡፡
ማረሚያ ቤቱ ያወጣው አዲስ የአፈጻጸም መመርያ በታራሚዎች ላይ ከፍተኛ ችግር የሚፈጥር ከመሆኑም በላይ፣ ሕገ መንግሥታዊ መብት የሚጋፋና በመታሰራቸው ምክንያት ንብረታቸው እንዲወድም፣ ቤተሰቦቻቸውን እንዳያገኙና እንዳይጠይቋቸው፣ በራሳቸውና በቤተሰቦቻቸው ላይ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ፣ ሥነ ልቦናዊና ማኅበራዊ ተፅዕኖ እንደሚያሳድርባቸው ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡
አንድ ታራሚ በመሠረታዊ መርህ ደረጃ በሕግ የተጠበቀ መብቱ ሊገደብ የሚችለው፣ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በሚያሳየው ያልተገባ ባህሪና የማረሚያ ቤቱን ሕግና ደንብ ንዶ ሲገኝ እንጂ፣ ከዓመታት በፊት በተቀጣበት ወንጀል መሆን እንደሌለበት ታራሚዎቹ ተናግረዋል፡፡ የክልል መንግሥታት የፌዴራል መንግሥቱ ያወጣቸውን ሕጐች የማስፈጸም ሕገ መንግሥታዊ መብት እንደተሰጣቸው የጠቆሙት ታራሚዎቹ፣ በመመርያው የዝውውር ዕገዳ የተጣለባቸው የወንጀል ዓይነቶች 90 በመቶ የሚሆኑት በክልሎች ፍርድ ቤትም የሚታዩና ውሳኔ የሚሰጥባቸው መሆናቸውንም ጠቁመዋል፡፡
የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ያወጣው የታራሚዎች የዝውውር መመርያ፣ ባጠፉት ጥፋት ተፀፅተው በመታረም ብቁ ዜጋ በመሆን ላይ ለሚገኙ ታራሚዎች በሕግ የተሰጣቸውን መብት የሚገድብ ከመሆኑም በላይ፣ የሕገ መንግሥቱን ድንጋጌና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 138/1999ን የሚቃረን በመሆኑ እንዲስተካከልላቸው ጠይቀዋል፡፡
ታራሚዎቹ የተቃወሙትን የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ያወጣውን የአፈጻጸም መመርያ በሚመለከት ማብራሪያ እንዲሰጡ የማረሚያ ቤቱን የሕዝብ ግንኙነት ጽሕፈት ቤት ረዳት ኃላፊ አቶ አዲሱ ጴጥሮስን ሪፖርተር አነጋግሯቸው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
አቶ አዲሱ በሰጡት ምላሽ፣ እንደገለጹት ‹‹የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስለፌዴራል ታራሚዎች አያያዝ ባወጣው ደንብ ቁጥር 138/1999 ማንኛውም ታራሚ የመጨረሻ ውሳኔ ካገኘና በሌላ ክስ የማይፈለግ ከሆነ፣ ቤተሰቦቹ በሚኖሩበት አካባቢ ወደሚገኘው ማረሚያ ቤት እንዲዛወር ካመለከተ ሊፈቀድለት ይችላል፤›› ሲል ‹‹ላይፈቀድለትም ይችላል ማለቱ ነው፤›› ብለዋል፡፡
ማረሚያ ቤቱ በመመርያው ላይ ዘርዝሮ ዝውውር የከለከላቸው የወንጀል ድርጊቶች ፈጻሚ ታራሚዎች ወደ ክልል ማረሚያ ቤቶች ቢላኩ፣ የፌዴራል ማረሚያ ቤቶችን ያህል ጥበቃ ሊደረግላቸውና ሊታረሙ ይችላሉ የሚል እምነት ባለመኖሩም ጭምር መሆኑን አቶ አዲሱ አስረድተዋል፡፡
በዚህ ጊዜ የታራሚዎች ዝውውር ዕግድ እንዲጣልበት የተደረገበትን ምክንያት እንዲያስረዱ የተጠየቁት አቶ አዲሱ፣ ምክንያቱ የሽብርተኝነት ወንጀል እየተስፋፋ በመምጣቱና ከሃይማኖት አክራሪነት ጋር የተያያዘ ወንጀል እየተስፋፋ መምጣቱና ሌሎችም ምክንያቶች እንዳሉ ገልጸዋል፡፡ ደንቡ ሲወጣ ደግሞ በመመርያ የሚወጣውን ዝርዝር ጉዳይ ታሳቢ በማድረግ በመሆኑ፣ የወጣው መመርያ ሊነቀፍ እንደማይገባው የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የሕዝብ ግንኙነት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊው አቶ አዲሱ ገልጸዋል፡፡
ሪፖርተር ያነጋገራቸው የሕግ ምሁራን ግን በወንጀል ሕጉም ሆነ በሌሎች የወንጀል ኃላፊነት የሚያስከትሉ ሕጎች ውስጥ የሃይማኖት አክራሪነት የሚባል ወንጀል እንደሌለ በመግለጽ፣ መመርያው ምን ለማት እንደፈለገ ግልጽ እንዳልሆነ አስረድተዋል፡፡
newspaper_ethiopia
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.-- 

Saturday, August 30, 2014

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያንን/ብሔራቸውን ነጻ ለማውጣት በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ የነጻ አውጪ ድርጅቶች ዝርዝር

 | 


  • 1782
     
    Share
Eriteria1- የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ( ደምሕት )
2 -የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦነግ – ዳውድ )
3- የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦነግ – ከማል )
4- የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦብነግ)
5- የግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሃይል
6- የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አርበኞች ግንባር
7- የድቡብ የእኩልነት እን የፍትህ ግንባር
8- የጋንቤላ ነጻ አውጪ ግንባር
9 – የቤንሻንጉል ነጻ አውጪ ግንባር
10 – አርዱፍ የአፋር ነጻ አውጪ
11- ጋደሌ የአፋር ነጻ አውጪ
12 -የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ንቅናቄ
13 – የአፋር ሕዝቦች ንቅናቄ
14 -የአፋር አንድነት ዲሞክራቲክ ፓርቲ
15 – ትንሳኤ አርበኞች ግንባር
16 – የአፋር ነጻ አውጪ የጋራ ሕብረት
እርስዎ የሚያውቁት ካለ ይጨምሩበት ።

-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--

Friday, August 29, 2014

AU and its failed member states


August 29, 2014
by Robele Ababya

Motivation for writing this article

Some 30 years ago I was at the French Embassy as one of the hundreds of invited guests on Bastille Day lavish celebration teemed with diplomats, government officials, distinguished personalities from civil societies and the business community. It was like a display of power French style.Dire effect of neglect by AU of TPLF abuses
A French acquaintance of mine amid our interesting conversation on various topics narrated to me about the French Revolution (1789 – 1799) and said he still didn’t understand why the necks of the King and the Queen were cut with the guillotine, implying that the human race still lives in dangerously insecure world of inequality where social justice is conspicuous by its absence.
I remembered the above conversation last week while I was glued to my TV watching a documentary featured on Aljazeera on the occasion of WWI Centenary. That war in which 14 million people died (9million soldiers and 5 million civilians) took 4 years (1914 – 1918), a period eight times more than the 6 months at first estimated by the warring side to declare the end of ‘the war to prevent all future wars. But WWII broke out only 23 years later in 1941 and ended in 1945 claiming the lives of 40 million combatants and civilians. Isn’t it disappointing that the goal for social justice has still not been hitherto achieved?!
One for the discussants on Aljazeera asked the pertinent question: what was it for that these wars fought? Indeed what was the rationale for fighting these wars given that morale rearmament is vanishing and sophisticated arms of destruction are flourishing in the 21st century? Smaller wars had been fought between the two world wars; several smaller wars have been fought and are in progress in the aftermath of WWII including in Africa ironically in the aftermath of the creation of the former OAU and its successor the AU. Is there guarantee to avert WWIII in the 21st century where the demand for allocating resources for the development of increasingly advanced military assets in preparation for future wars? Is Ukraine going to be the flashpoint WWIII?
It is heartbreaking that the decisions made to go to war to end future wars did not yield the desired fruit; revolutions to prevent future revolutions did not work. The end to wars and political upheavals is not in sight! One would only pray that the scale of destruction will not be catastrophic.
Unable to learn from history that there is no lasting military solution to social injustice, AU members states fight each other squandering huge amounts out of their meager resources on military hardware, facilities and personnel either to fight each other or silence legitimate internal dissent. It is both legally and morally inadmissible that African leaders plunge their respective countries in senseless arms race at the expense of basic social services. The arms race in the Horn of Africa as an example and the scaring number of failed AU member states motivated the writing of this piece.

Snapshot on the arms race in the Horn of Africa

Emperor Menilik II vanquished the vastly superior Italian Army in the 1896 war at Adwa with his poorly armed wholly militia army equipped with home-made swords, spears, et al supplemented by rifles procured from European powers who were competing to supply such fire arms to other warlords including Emperor Yohannes IV.
Menilik II’s victory at Adwa not only shocked European powers forcing them to recognize Ethiopia as an independent sovereign country, but also became a beacon of hope for all black people in the Diaspora struggling for emancipation.
The beloved Menilik II had no desire of establishing a standing regular army arguing financing of such an establishment would be expensive to the poor taxpayers in the first instance and that soldiers thereunder will violate basic human rights of civilians by engaging in looting and raping not to mention destabilizing the government. So the task of creating a standing modern army became the responsibility of Emperor Haileselassie I, although some of the arguments of Menilik II are still valid today.
So, Emperor Haileselassie embarked on the lofty task by opening the first military training center at Holeta located 40 kilometers south-west of Addis Ababa. This effort was cut short by the invasion of Ethiopia by Fascist Italy in 1935.
The effort of building modern regular defense force – including ground force, air force and navy – took center-stage upon the victorious return of the Emperor to His capital city Addis Ababa in 1945. The national defense militia force was organized at a later time in substantial scale. The Monarch did His best in bolstering the army in His capacity as its Commander-in-Chief until His overthrow in 1977 ironically by the successors of army He founded. The octogenarian Monarch lacked either the courage or wisdom or both to call it quits in time and became a victim of disgrace of the Derg, which exceeded its mandate in most cases.
The genesis of the arms race in the Horn of Africa on a significant scale is reasonably attributable to the territorial claims of Somalia blinded by its leaders with their pipedream of creating “Greater Somalia” symbolized by five stars imprinted on their national flag. This mad ambition required acquisition of modern military weapons from socialist countries posing as converts to Marxist-Leninist ideology. The defunct USSR agreed and inundated the regime of Ziade Bear with a generous supply of fire arms including tanks artillery, jet bombers as well as jet fighter airplanes. The balance of military power changed instantly in favor of Somalia thus making Ethiopia nervous for the time being.
I recall the time that five senior officers including me were assigned the task of assessing the new threat posed by Somalia. There was sufficient top secret intelligence made available by the Ethiopian Ambassador in Mogadishu to supplement our own gathered by the intelligence unit of the Air Force.
The Emperor went on a mission to Washington to see the then Secretary of Defense Mr. McNamara and present a request for provision of military assets worth millions of US$ including the requirements separately compiled by the Ground Forces and the Navy. The package included a Squadron of Phantom Bombers.
The Secretary declined to agree with the request on grounds that it will not be in the interest of the region to encourage arms race. The Emperor was disappointed and travelled straight to the Ex-USSSR with similar request for arms, which the Kremlin authorities declined to provide, but offered development aid to the tune of 400 million rubles instead. Ethiopia was forced to go elsewhere to shop for fire arms.
The Ethiopian Revolution broke out suddenly in February 1974. The left leaning policy of the Derg regime disappointed the USA, but endeared the Junta to the Kremlin which for fear of Maoists usurping the new political landscape, rushed with the offer to provide substantial military assets including Mig-21bis. I recall a young Russian Major coming to my office with a request to facilitate a meeting with the rank and file Air Force personnel to announce the offer, which was enthusiastically accepted in the face of the Carter Administration refusing to supply the US$ 100 million worth of military equipment paid for by poor Ethiopia for self-defense.
Thus the arms race in the Horn of Africa took a dramatic turn increasing significantly on unprecedented scale emboldening the Ziade Bare army to invade Ethiopia in 1977. I know so because I signed for one of the agreements with the ex-USSR government on behalf of Ethiopia at the time of the invasion.
Somalia lost the war eventually, thanks in particular to the effective assistance of the USSR and Cuba. But Mengistu got his priorities wrong in refusing to adopt an inclusive government and mixed-economic policy supported both by the USSR and the Western powers. Thus he lost trust with the Ethiopian people and suffered humiliating defeat by the combined force of TPLF rebels and the separatist Shabia, the latter playing a major role with the help of Arab reactionaries.
Mengistu’s ignorance and stubbornness led him into fleeing the country leaving a huge army in disarray and out of existence eventually. Thus the glory and indispensable long tradition of the Ethiopian army built over more than 70 years abruptly ended; it was once branded by President Gorbachev as a mighty force in Africa. This is a classic example of ruins that dictators leave behind when they fall from power – a lesson to heed for African tyrants!
The present situation is that Somalia is a failed state; Eritrea is a pariah state; Isaias has lost his Air Force; desertion is rampant within the defense force of the EPRDF regime. These are the fruits of the detrimental effect of the arms race in the absence of moral rearmament. In retrospect I applaud Robert McNamara for his advice not to start arms race in the Horn of Africa.

Rethinking African defense doctrine/Strategy

The big powers, scrambling for strategic natural resources, are engaged in cut throat competition everywhere on the planet Earth and beyond. They are competing for military supremacy in wars of future wars involving advanced weapons hard to imagine. The gap between reality and what we see about warfare on future wars or read in science fictions is narrowing to the point of vanishing. On the other hand, the techno-scientific gap between the big industrial world and Africa is widening – forcing African tyrants to procure phased-out military assets. The question is to fight whom?
The entire military assets of the Africa combined are no match for a single neo-colonial power in the event of war. In any case colonial masters have no appetite for engaging in direct war. The African leaders will fight each other while suppressing their people to the point of running out of resources. The colonial masters will come back with their drilling equipment to extract the rich minerals of the African continent.

Failed African states

Here is a list in descending order of 25 failed states (with Somalia at the bottom) in our global village from Google:- Eritrea, Liberia, North Korea, Uganda, Syria, Burundi, Ethiopia, Niger, Kenya, Nigeria, Guinea Bissau, Guinea, Pakistan, Côte D’Ivoire, Zimbabwe, Central African Republic, Haiti, Afghanistan, Yemen, Chad, South Sudan, Sudan, Congo, Somalia.

It is interesting to note that:-

• Sadly, 18 out of 25 of these states are in Africa;
• Failed state Ethiopia shares borders with other five failed states including Somalia, Eritrea, Kenya, Sudan, South Sudan making the region a fertile ground for acts of terrorism by Al Shabab, Al Qaeda, Boko Haram, and ISIS; the region is certainly a volatile area ready to explode;
• Corruption is rampant in Uganda as admitted by its government, but it is not a failed state in my opinion;
• Kenya is not a failed state albeit corrupt in my opinion;
• Tiny Djibouti and war-torn Iraq are failed states in my opinion, but they are not in the list
• All the above 18 African states are beset by endemic corruption.
In view of the foregoing short analysis under this section, the onus is on AU leaders in rethinking African defense doctrine because expenditure on security and defense has up to the present proved an intolerable hemorrhage on natural resources without being able to avert several internal battles fought within the continent since the creation of the ex-OAU and its successor the AU. It would be prudent to consider in all seriousness the concerns of Emperor Menilik II about heavy expenditure on regular army prone to abuse of human rights.

Glimmer of hope

There is hope that some of the leaders in the East African Community like the PanAfricanist President Yoweri Museveni, President Uhuru Kenyatta of Kenya, and President Paul Kagame of Rwanda have the ability, courage, and vision to root out corruption, provide good governance, and engender growth by overcoming bureaucracy.
President Kenyatta addressing a huge crowd of mainly youths from the Community that were gathered at Kampala Parents School in Naguru, in the school’s auditorium on the occasion of the 4th Pakasa Form on 24/08/14. In his inspirational address enthusiastically punctuated by applause, he articulated the vision of a new self-reliant Community admitting the dismal performance of the continent in the last 50 years; he underscored that governance has been bad in all these years and needs to change for the better. The President made several salient points each of which was received with warm applause of the intelligent youths who were unafraid to pose tough questions which he answered frankly to the delight of the audience. Self-reliance was what I wanted to hear in a long time and I heard it enunciated by the President to the delight of the audience in the auditorium and me watching it on TV outside in the city!
Ethiopia actively supported Kenyan freedom fighters liberation movements in Africa. Kenya was a haven for Ethiopian refugees during the Italian Fascist invasion. I ask His Excellency President Kenyatta why not recently during His reign when bad governance is at its worst in Ethiopia forcing young Ethiopians to flee to neighboring states are not welcome? The TPLF/EPRDF racist regime in Addis Ababa is a menace to regional peace. Therefore, I implore President Kenyatta and his colleagues President Museveni and President Kagame to use their influence under “Peer Rating Mechanism” to ask EPRDF top leaders to discard their divisive archaic tribal policy in Ethiopia that is bound to destabilize the region.
I salute the trio for the sterling job they are doing to address the problems of their Community transparently on the PAKASA Forum; their determination to usher in a self-reliant Africa with its patriotic citizens taking the center-stage is laudable. President Museveni’s heroic stand not to take orders from outside is inspiring. So there is a glimmer of hope for self-sustaining economic growth in an environment of democracy both at the same time in EAC that would serve as example to others on the continent.
Finally, I call on AU leaders with due respect:-
• to allow unfettered freedom of expression in all its forms in their respective countries; to condemn the EPRDF regime for muzzling press freedom and forcing the exodus of journalists; it is unacceptable that the regime that claimed 99.6% ‘victory’ in election 2010 is bent on cracking down so heavily on the free media while it holds monopoly over all pillars of democracy including the press; to embrace the cause of the Ethiopian people demanding regime change;
• to instill the spirit of patriotism in the minds of the African youth through incorruptible exemplary leadership; to do the needful to avert war between African youths; to prevent the probability of armed clash between Ethiopia and Eritrea that the EPRDF regime is vowing to start;
• to note that 18 out of 25 failed states are in Africa necessitating urgent corrective action to reverse the sad situation by sincerely and openly applying their “Peer Rating Mechanism”;
• to condemn in the strongest terms the deadly virus of “apartheid policy” of the TPLF/EPRDF brutal regime from spreading further throughout the African continent;
• to combat “corruption” and “militarization” as deadly issues in our global village causing youth unemployment and failure to usher in liberty, democracy and prosperity;
• to note and condemn the building of personality cult of a genocidal and racist tyrant, Meles Zenawi, in the 21st century in the 2nd poorest country on earth at the expense of the suffering masses of Ethiopia.
• to demand the unconditional release of all political prisoners and prisoners of conscience in Ethiopia – including:- Andualem Aragie, Eskinder Nega, Andargachew Tsige, Abraha Desta, Bekele Gerba, Reeyot Alemu, Leaders of the Ethiopian Muslims, the 9 bloggers and 3 Journalists, et al!
To my fellow citizens: – The brutal murder of the 18-year old African-American Michael Brown evoked a shockwave of protest demonstration across the USA for several days; on the contrary, we Ethiopians did little to stem the grave human rights violation including genocide, murders and massive arrests of citizens by TPLF/EPRDF security forces under the direct command and control of tyrant Meles Zenawi and his successors. Shame on us that we have been unable to break the backbone of the puppet brutal regime in the last 23 years!
Call on EPRDF defense and security: – Junior members have nothing to fear in coming on the side of the Ethiopian people and thereby make history by collaborating with the opposition and thereby averting costly catastrophe of internecine; start with disobeying the corrupt wealthy Generals and show your loyalty to the Ethiopian people.
In closing, I am convinced that there is no end in sight to the quest for social justice as long as the appalling “man’s inhumanity to man” exists. Morale rearmament is by far the best option to achieve the goal of social justice.
LONG LIVE ETHIOPIA!!!
rababya@gmail.com                 source  ecadforum

‹‹ለግራዚያኒ ዘብ የቆመው ኢህአዴግ እንዴት ኢትዮጵያዊ ይባላል?››


ሰልጣኝ ተማሪዎች
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስልጠና ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ተማሪዎች ጠንከር ያሉ ጥያቄዎችን ማንሳት መቀጠላቸውን ሰልጣኞቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ባለፉት የስልጠና ጊዜያት ኢህአዴግን ላለፉት 23 አመታት አይተነው ለውጥ ስላላመጣ ስልጣን ሊለቅ ይገባል፣ የአሰብ ወደብ ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው፣ የሸክ ኑሩ ግድያ ሴራ ነው፣ የባህርዳሩ ግጭት የብአዴን ሴራ ነው የመሳሰሉት ጥያቄዎች መነሳታቸው ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች እየተነሱ መሆናቸውን ሰልጣኞቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
• ‹‹ተቃዋሚዎችን እያሰራችሁ እንዴት ተቃዋሚ የለም ትላላችሁ››
• ተማሪዎቹን በፖሊስና ደህንነት እያሸማቀቁ ነው
• ‹‹ብሄራዊ ቋንቋ የሌላት አገር ሉዓላዊ ልትባል አትችልም››
• ‹‹አንቀጽ 39 ከህገ መንግስቱ ይውጣ››
• ‹‹ለግራዚያኒ ዘብ የቆመው ኢህአዴግ እንዴት ኢትዮጵያዊ ይባላል?
• ተማሪዎቹን በፖሊስና ደህንነት እያሸማቀቁ ነው
የህገ መንግስት ማሻሻያ
በደብረማርዎስ ከተማ የሚሰለጥኑ ተማሪዎች ህገ መንግስቱ ማሻሻያ እንዲደረግበት ጠይቀዋል፡፡ በተለይም አንቀጽ 39 ‹‹የኢትዮጵያ ህዝብ መካከል ልዩነት ለመፍጠር ህገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠ አንቀጽ በመሆኑ ህገ መንግስቱን ለማሻሻል የተቀመጡት ውጣ ውረዶች ሳይገድቡት ከህገ መንግስቱ ሊወጣ ይገባል›› ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል ‹‹አንቀጽ 39 እንዲሁ ከሚቀየር የኢትዮጵያ ህዝብ ህዝበ ውሳኔ አድርጎበት ከህገ መንግስቱ ቢወጣም የተሻለ ነው፡፡›› የሚል ሀሳብ ያቀረቡ እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡
ብሄራዊ ቋንቋ
ተማሪዎቹ ‹‹ኢትዮጵያን ያህል አገር ለምን ብሄራዊ ቋንቋ አይኖራትም?›› ብለው የጠየቁ ሲሆን አሰልጣኞቹ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ቋንቋ የሌላት መሆኑን ተናግረው ከማለፍ ውጭ ለጥያቄው መልስ መስጠት እንደተቸገሩ ሰልጣኞቹ ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ በበኩላቸው ‹‹ህገ መንግስቱ ሲረቀቅ የብሄራዊ ቋንቋ ጉዳይ የተረሳው ሆን ተብሎ ነው፡፡ ብሄራዊ ቋንቋ የሌላት አገር ከሌሎች ብሄራዊ ቋንቋ ካላቸው አገራት ጋር እኩል ሉዓላዊ ልትሆን አትችልም›› ሲሉ አስተያየት መስጠታቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ኢህአዴግ ኢትዮጵያዊ ነው?
መጋቢት 6/2005 ዓ.ም ሰማያዊ ፓርቲ፣ ባለራይ ወጣቶችና በአቶ ታዴዎስ ታንቱ የተመራ የአገር ተቆርቋሪ አካል ለግራዚያኒ የቆመውን መታሰቢያ ተቃውሞ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የሰማዕታቱ ሀውልት ጀምሮ ወደ ጣሊያን ኤምባሲ የሚያመራ ሰልፍ ጠርቶ ነበር፡፡ ይሁንና ሰልፉ ከመጀመሩ በፊት ፖሊስ ሰልፉን በኃይል በመበተን ተሳታፊዎቹን ማሰሩ ይታወቃል፡፡ በስልጠና ላይ የሚገኙት ተማሪዎቹም ‹‹ኢትዮጵያውያንን የቀጠፈውን የቅኝ ገዥ ጀኔራል ላይ ተቃውሞ እንዳይነሳ የፈለገና፣ በእሱ ላይ ተቃውሞ ሰልፍ ለመውጣት የሞከሩትን የደበደበና ያሰረው ኢህአዴግ እንዴት ኢትዮጵያዊ ሊባል ይችላል? ኢህአዴግ ለግራዚያኒ ጠበቃ ቆሞ እንዴት ኢትዮጵያዊ ይባላል?›› ይባላል የሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡
ተቃዋሚዎቹን እያሰራችሁ
አሰልጣኞች ተቃዋሚ ፓርቲዎች በሰላማዊ ሰልፍም ሆነ በሌሎች አጋጣሚዎች የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች ትክክል አለመሆናቸውን የገለጹ ሲሆን ጠንካራ ተቃዋሚ ፓርቲ እንደሌለም ተገልጾአል፡፡ በተቃራኒው ተማሪዎቹ በተቃዋሚዎቹ ላይ የሚደርስባቸውን ጫና እና የታሰሩትንም በምሳሌነት በማንሳት ‹‹ተቃዋሚዎቹን እያሰራች እንዴት ተቃዋሚ የለም ትላላችሁ? የሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡ ኢህአዴግ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅዱን ለማሳካት አቅም እንደሌለውና አፋኝ እንደሆነ የሚገልጹ አስተያየቶችንም ተነስተዋል፡፡
ተማሪዎቹን ማሸማቀቁ ቀጥሏል
በተለያዩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲዎች የሚገኙ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ጥያቄ እንዳይጠይቁ ማሸማቀቁ እንደቀጠለ ነው ተባለ፡፡ በተለይ በልደታ ግቢ በመሰልጠን ላይ የሚገኙ ተማሪዎች ጥያቄ ሲጠይቁም ሆነ አስተያየት ሲሰጡ ስለማንነታቸው አላስፈላጊ ዝርዝር ጥያቄዎችን እየተጠየቁ እንደሆነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ኢህአዴግን ደግፈው የሚከራከሩ ተማሪዎች ቁጥር በማነሱ ፖሊስና ደህንነቶች ሲቪል መስለው እንደሚከራከሩና የሚጠይቁትንና ጠንካራ አስተያየት የሚሰጡትን ተማሪዎች ለብቻቸው እየጠሩ እያሸማቀቁ መሆኑ ታውቋል፡፡
ከአፈናው በተጨማሪ በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች የሚሰለጥኑትን ተማሪዎችን በመደለያነት ሙዚቃ፣ ከፍተኛ ወጭ የወጣበት ምግብና የመዝናኛ ምሽቶች እየተደረጉላቸው መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል ፡፡በሌላ በኩል በመላ አገሪቱ በስልጠና ላይ ለሚገኙት ተማሪዎች ስልጠና የሚሰጡት ከወራት በፊት በመቀሌ ስልጠና የተሰጣቸው የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

ቄሮ፡ የኦሮሞ፡ ወጣቶች፡ ለነፃነት፡ ንቅናቄ፡ ድምፅ፡ የሳምንቱ፡ ዜና – Hagayya 27, 2014 Sagalee ...

Thursday, August 28, 2014

VOA investigating distortion allegations

VOA investigating distortion allegations

August 28, 2014
by Dawit Ashenafi
(Addis Voice) – The Voice of America says it has begun a thorough investigation into allegations of deliberate distortions at VOA Amharic Service. Kevin Lynch, assistant director of public relations at VOA, confirmed that the allegations are being probed in earnest.The director of VOA, David Esor
The director of VOA, David Esor,also noted in a statement he gave to VOA Horn of Africa that he would do everything in his power to address the complaints.
The director was quoted by VOA Tigrigna as saying: “When complaints are made that VOA has made errors, we investigate the report, and if an error has been made, we correct the error, and apologize for it.”
Scores of Ethiopian-Americans staged a protest rally on Monday in Washington D.C. at the State Department. The protesters demanded, among other things, that VOA should stop the deliberate distortions at VOA by the sympathizers of the tyrannical regime in Ethiopia. The protest followed a recent VOA Amharic report by Henok Semaegzer Fente that allegedly misrepresented and deliberately distorted facts related to the revocation of an honor bestowed on him by Azusa Pacific University.
David Ensor, who worked for NPR, ABC News and CNN in his long spanning journalism career, sworn in as the 28th Director of the Voice of America on June 16, 2011, it was learned.
—-
The following was originally reported by VOA Tigrigna on August 25th, as summarized and translated by Abraha Belai of Ethiomedia.
VOA Director David Ensor has responded to the protest held at the State Department. He said there were resentments being heard from every direction, and he would work to his full capacity to address the issues.
The director said VOA should feel whether it is content with the coverage of the Ethiopian Diaspora protest rally in front of the State Department.
We respect the complaints one of which is how VOA Horn of Africa section covers events with fairness. All VOA Language Services work hard to make their reports as fair as possible. VOA occasionally sees the fairness of its reports and services vis-a-vis its reputation.
On some occasions, VOA has drawn critical complaints from several sources who complain that the VOA reporting lacks honesty and balance.
While the [Ethiopian] government accuses us of “broadcasting extremely harsh news reports,” the Ethiopian Diaspora on their part accuse us of broadcasting reports not critical enough on the government [in Ethiopia].
No matter from where the complaint comes, the director said, VOA should work diligently and attentively. When complaints are made that we have made errors, we investigate the report, and if an error has been made, we correct the error, and apologize for it.
We thank all those who stand by our side during our broadcasting services of news and information, David Ensor said.
The protesting members of the Diaspora at State Department complained VOA, instead of serving the people, broadcasts reports that kill the hopes of the people, and this has been felt since some individuals joined VOA.
source ecadf

Tuesday, August 26, 2014

በአፋሮች መካከል በተነሳ የድንበር ይገባኛል ግጭት የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተዘገበ


 

  • 48
     
    Share
(ዘ-ሐበሻ) አሁን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በአፋር ክልል በሰሜን ዞን በኮናባ ወረዳ ነዋሪዎች እና በትግራይ ክልል የአፅቢ ወንባርታ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል ግጭት የተቀሰቀሰ ሲሆን እስካሁን የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተዘግቧል።
(የሕወሓት መንግስት ኢትዮጵያን የሚያስ ተዳድርበት ካርታ)
(የሕወሓት መንግስት ኢትዮጵያን የሚያስ ተዳድርበት ካርታ)

አኩ ኢቢን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ ባደረሰው መረጃ በኮናባ ወረዳ የዋህደስ ቀበለ አፋሮችና በአፅቢ ወረዳ ኦሳት ቁሼት ከ1 አመት በፊት የድምበር ይገባኛል ያለመገግባባት የነበረ መሆኑ በተደጋጋሚ የተዘገበ ሲሆን ዛሬ ከሳዓት በኋላ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 8:30 ጀምሮ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ ግጭት ላይ ይገኛሉ።
በድንበር ይገባኛል ግጭት የተነሳ በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ከዚህ ቀደም ንጹሃን ዜጎች ሕይወት ማለፉ የሚታወስ ሲሆን አሁንም በአፋሮች እና በትግራዮች መካከል የተነሳው ግጭት ሥርዓቱ የፈጠረው የዘረኝነት አስተዳደር ውጤት ነው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ።
ለዘ-ሐበሻ መረጃውን ያደረሰው አኩ ኢቢን ኮናባ መተው እየተዋጉ ያሉት የወታደር ልብስ የለበሱ የሚሊሻ አባላት ናቸው ሲል እስካሁን በዚህ ግጭት 1 ሰው ሲሞት 2 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ብሏል። በሞተው ሰው ጉዳይ ዘ-ሐበሻ ከመንግስት ወገኖች ለማጣራት ያደረገችው ጥረት ባይሳካም የድንበር ግጭቱን ለማብረድ ከመንግስት በኩል እየተደረገ ያለው ዝግመተኛ ሥራ የአካባቢውን ነዋሪዎች እንዳስቆጣ ምንጮች ገልጸውልናል።
በዚህ ግጭት ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እንመለሳለን።
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--

‹‹የፀረ ሽብር ህጉ ሰለባዎች ››በፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል የተዘጋጀ ዶክመንታሪ

ሥርዓቱን ለ 20ዓመት አይተነዋል መቀየር አለበት! የተማሪዎች ተቃውሞ

 | 
  • 407
     
    Share
የኢትዮጵያ የባህር በር ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው
የኢኮኖሚ እደገቱ እውነት አይደለም
የትምህርት ስርዓቱ ወድቋል
የተማረ ሰው ክብር አይሰጠውም
Ethiopian_Student_Protest_2001_02አዲስ አበባ ውስጥ ሳውዝ ካምፓስ (ልደታ)፣ አቃቂ (AASTU)፣ ፍቼ የግብርና ኮሌጅ፣ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ፣ የአዲስ አበባ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስት ትምህርት ክፍልና ሌሎችም አካባቢዎች ከነሃሴ 15 ጀምሮ ስልጠና ላይ የሚገኙ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን እንደቀጠሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ ገዥው ፓርቲ አለ በሚለው እድገት፣ የባህር በር፣ የተማረው የማህበረሰብ በሚደርስበት በደል፣ የትምህርት ጥራት፣ የመምህራን የእውቀት ደረጃ ማነስ፣ ድህነትና አጠቃላይ ኢኮኖሚ ውድቀት ላይ ጠንከር ያለ አስተያየትና ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ተገልጾአል፡፡
የኢኮኖሚ እድገት
ተቃውሞ ከገጠማቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ እድገት አለ የለም የሚለው ሲሆን ተማሪዎቹ ‹‹በአክሱም ዘመን ገናና የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በኢኮኖሚው መስክ ጭራ›› መሆኗን በመግለጽ እድገቱ አለ መባሉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጨምረውም “በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ የማይችል ማህበረሰብ ይዘን አድገናል ማለት አንችልም” በሚል እድገት አለመኖሩን ተከራክረዋል፡፡ “ሀገራችን ውስጥ የምግብ፣ የቤት፣ የትምህርት፣ የኔትወርክና ሌሎች ችግሮች አሉ፡፡ ስኳርና ዘይት ለመግዛት ህዝብ ቀበሌ ተሰልፎ ነው የሚውለው፡፡ በ400 ብር ደምወዝ ቤተሰብ የሚያስተዳድር ህዝብ ያለባት ሀገር የሌሎችን እድገት ፈዛ እያየች ያለችን ሀገር አድጋለች ልንል አይገባም” ማለታቸው ተገልጾአል፡፡
በተመሳሳይም “2 በመቶ የሚሆነው የአሜሪካ አርሶ አደር ዓለምን በሚመግብበት በአሁኑ ወቅት 85 በመቶ አርሶ አደር ይዘን ለምን እንራባለን?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውንም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎቹ “አድገናል ብለን ራሳችን ማወዳደር ያለብን ከ40 አመት ከነበረ ስርዓት ጋር መሆን የለበትም፡፡ እድገታችን መለካት ካለበት ከሌሎች አገራት ጋር ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት በ2020 እንመደባለን ከተባለ መንግስት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ይህን ስርዓት ለ20 አመት አይተነዋል፡፡ ባለፉት አመታት ለውጥ ሊያመጣ አልቻለምና በ2020ም ለውጥ ያመጣል ብለን አንጠብቅም” የሚል ጠንካር ያለ ሀሳብም አቅርበዋል፡፡
እድገት ላይ ነው የሚባለው የኮንስትራክሽን ዘርፍ የጥራት ደረጃው ዝቅተኛ መሆኑን በተለይ በዘርፉ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ “እድገት የምንለው የህንጻዎችን ወደላይ ማደግ ወይንም መብዛት ሳይሆን የማህበረሰቡን አስተሳሰብና አኗኗር ዘይቤ መቀየር ነው” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ በስልጠናው ወቅት ገዥው ፓርቲ የቻይናን ፈለግ ተከትሎ እድገት ማስመዝገቡን በመቃወም “ቻይና ከ2.3 እስከ 2.7 በመቶ እያደገች እንደሆነ ይነገራል፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለች የተባለችው ኢትዮጵያ ከ11.2 በመቶ በላይ አደገች ነው የሚባለው ከየት አምጥተነው ነው? ወይስ እንደ ቀን አቆጣጠራችን እድገታችንም ይለያያል?” ሲሉም አሰልጣኖቹን ጠይቀዋል፡፡
የባህር በር
ተማሪዎቹ ለኤርትራ መሰጠቱ አግባብ እንዳልሆነ፣ የባህር በርና ወደቡ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት፣ ደህንነትና ታሪክ አንጻር አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ገዥው ፓርቲ በባህር በር ላይ ያለውን አቋምና ፈጸመ ያሉትን ስህተት ተችተዋል፡፡ ወደብ አልባ በመሆናችን ኢኮኖሚያችን ወደኋላ መቅረቱንም አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል “በአገራችን የሚመረቱ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡት ከውጭ ከተላከው ሲተርፍ ነው” በማለት በኤክስፖርት ዘርፍ ያለውን ችግር፣ አገር ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የኑሮ ውድነት ከዚሁ ችግር መመንጨቱን ጠቅሰዋል፡፡
የትምህርት ጥራት
ተማሪዎቹ የራሳቸውን ተሞክሮ በመጥቀስ የትምህርት ስርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመከራከሪያነት አቅርበዋል፡፡ “ለተማረ ሰው ክብር እየተሰጠ አይደለም” በሚል የእነሱም እጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም “የሚያስተምሩን አስተማሪዎች የእውቀት ደረጃ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው፡፡ በየ ዩኒቨርሲቲው በአመራር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች እውቀት የላቸውም” በማለት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደቀነውን አደጋ አንስተዋል፡፡
ዲግሪ ይዘው በስራ ፈጠራ ስም በጥቃቅንና አነስተኛ እንዲደራጁ የሚደረገውን የተቃወሙት ተማሪዎቹ “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተደራጅተው ካፌ ከፈቱ፣ ኮብልስቶን አነጠፉ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መማር አያስፈልገውም፡፡ ይህን ስራ ለመስራት የሶስት ወር ስልጠና በቂ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲ መማር ባላስፈለ” ሲሉ የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት እንደገጠመው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
(ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ – ፎቶ ከፋይል ማህደር)
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--