Thursday, November 27, 2014

የስደተኞትና የስደት ተመላሾች እጣ


  • 148
     
    Share
8EF5BDEB-55F0-43A5-9205-44A05F770A20_w268_r1የምሥራቅ አፍሪቃ አገሮች በስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ላይ የጋራ ራእይና እቅድ እንዲኖራቸው ለማስቻል የታለመ የሁለት ቀናት ውይይት አዲስ አበባ ላይ ተጀምሯል።
የስደተኞች አንዷ መዳረሻ በሆነችው የወቅቱ የአውሮፓ ሕብረት ፕሬዝዳንት ጣልያን አነሳሽነት የሚካሄደው ይህ ውይይት በአጭርና ረዥም ጊዜ የሚተገበሩ ግቦች ያመነጫል፤ ተብሎ ተጠብቋል።
በሌላ በኩል የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ ትላንት ስትራስበርግ ፈረንሳይ ለሚገኙት የአዉሮፓ ፓርላማና ምክር ቤት ንግግር ስለ ስደተኞች ሰብአዊ መብትና መከበር ንግግር አድርገዋል።
ርእስ ሊቃነ-ጳጳሱ በሁለቱም ስፍራዎች ባደረጉት ንግግር አዉሮፓ የቆመችለትን ሰብአዊ መብትን የማክበር መርህና ዴሞክራዊ እንድታከብር ጥሪ አድርገዋል።
የሮማው ርዕሰ ሊቃነ-ጳጳስ በ25 ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአውሮፓ ተቋማት ያሰሙትን ንግግር ተንተርሶ የተጠናቀረ ዘገባ ነው።
በርዕሶቹ ላይ የተጠናቀሩትን የእነዚህን ዘገባዎች ዝርዝር ከዚህ ያድምጡ፤
Source:: voanews
-- Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.--

No comments: