Friday, May 15, 2015

በቴፒ 5 ሰዎች ተገደሉ

Amharic

በጋምቤላና ደቡብ ክልል ድንበር አካባቢ የሪ በምትባል ቀበሌ 7 ሰዎች በተገደሉ ማግስት ሌሎች 5 ሰዎች ደግሞ በቴፒ ከተማ እንድሪስ ቀበሌ ውስጥ ከሌሊቱ 8 ሰአት ላይ በጥይት ተደብድበው መሞታቸውን የአካባቢው ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል።
የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት ከሟቾቹ መካከል አባትና ልጅ ይገኙበታል። ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ ገዳዮቹ ፖሊሶች ናቸው። ነዋሪዎች እንደሚሉት ሰዎቹ ይተገደሉት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አማጽያንን ያስጠጋሉ፣ ይደግፋሉ ተብለው ነው። ኢሳት ለከተማው ፖሊስ በመደወል ለማጣራት ሙከራ ቢያደርግም አልተሳካም።
ኢሳት ከሶስት ቀናት በፊት “ከመስከረም ወር ጀምሮ በቴፒና አካባቢዋ ያለው ግጭት ተባብሶ በመቀጠሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ስጋት ላይ መውደቃቸውንም፣ በእየለቱ በከተማዋ ውስጥ የጥይት ድምጽ እንደሚሰማና በርካታ ቁጥር ያላቸው የሸኮ መዠንገር ነዋሪዎች እየፈለሱ ወደ ቴፒ ከተማ በመግባት ላይ መሆናቸውን ” ዘግቦ ነበር።
ነዋሪዎች ጸጥታውን የሚያስከብርልን ሃይል አጥተናል በማለት በተደጋጋሚ አቤቱታ ያሰማሉ።            

No comments: