Thursday, October 29, 2015

ቴድሮስ አድሃኖም የት ናቸው? – አንዳርጋቸው ጽጌ ‹‹በእንግሊዝ ቅበሩኝ ››

ቴድሮስ አድሃኖም የት ናቸው? – አንዳርጋቸው ጽጌ ‹‹በእንግሊዝ ቅበሩኝ ››

  • 2010
     
    Share
ከዳዊት ሰለሞን
የሶስት ልጆች አባት የሆኑት የግንቦት ሰባቱ ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡና ያሉበት ሁኔታ ሳይታወቅ 16 ወራቶች ተቆጥረዋል፤ በወህኒ ቤት እንዳሉም ሊገደሉ እንደሚችሉ መናገራቸው ተሰምቷል፡፡
andargachew new picture
አንዳርጋቸው ይበሩበት የነበረ አውሮፕላን የመን ሰንዓ ማረፉን ተከትሎ ታፍነው ለኢትዮጵያ መንግስት ተላልፈው የተሰጡት በወርሃ ሰኔ 2014 መሆኑ አይዘነጋም፡፡ለአንድ ዓመት ያህል ድብቅ በሆነ እስር ቤት ውስጥ ለወራቶች ምርመራ ሲደረግባቸው የቆዩት አንዲ በቅርቡ ወደ መደበኛ ወህኒ ቤት መዘዋወራቸው ቢነገርም እስካሁን በውል ያሉበት ሁኔታ አይታወቅም፡፡ይገኙበታል የተባለው የቃሊቲ ወህኒ ቤት ኃላፊዎችም አንዳርጋቸውን ለምስክርነት ጠርቶ ለነበረ ፍርድ ቤት አንዳርጋቸው በወህኒ ቤቱ እንደማይገኙ አስታውቋል፡፡
አንዳርጋቸው በሌሉበት በቀረበባቸው ክስ በሁለት አጋጣሚዎች የእድሜ ልክና የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው መሆኑ አይዘነጋም፡፡እጃቸው ከተያዘበት ወቅት ጀምሮም የአንዳርጋቸው ቤተሰቦች ያቀረቡት የጉብኝት ጥያቄ አልተሳካም፣ጠበቃ ለማቆም የተደረገው ሙከራም እንዲሁ ፣በህግ ፊት እንዲቀርቡ ባለመደረጋቸውም ከዚህ ቀደም የተላለፈባቸውን ፍርድ በምን መንገድ ሊተገብሩት እንዳሰቡ አሳሪዎቻቸው ግልጽ አላደረጉም የእንግሊዙ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሪፕራይቭ ጠበቆቹ አንዳርጋቸውን እንዲጎበኙ ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል፡፡
አሁን አንዳርጋቸው በቅርቡ ሊገደሉ እንደሚችሉ ስጋት የገባቸው በመሆኑ ለእንግሊዝ መንግስት ‹‹በእንግሊዝ ስርዓተ ቀብራቸው እንደሚፈጸም እንዲያረጋግጡላቸው ጠይቀዋል፡፡ለንደን ለሚገኙ ልጆቻቸው ባስተላለፉት መልእክትም ‹‹ጎበዞች››እንዲሆኑ መክረዋል፡፡
በቅርቡ በጣም ውስን ለሆኑ ደቂቃዎች በኢትዮጵያ የእንግሊዝ አምባሳደርን ያገኙት አንዳርጋቸው ለአምባሳደሩ
–የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለወራት ከወህኒ ቤት ክፍላቸው እንዳይወጡ መከልከላቸውን
–የእስረኛ ቁጥር እንዳልተሰጣቸውን አሳሪዎቻቸው የእስር ምክንያታቸውን ወይም የተወነጀሉበትን ጉዳይ ያልነገሯቸው መሆኑን
–ጠበቃ ለማግኘት ጠይቀው መከልከላቸውን
— በህመም ላይ የሚገኙ ቢሆንም ህክምና እንዳያገኙ መደረጋቸውን
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአንዳርጋቸውን ኢሰብአዊ አያያዝ በመቃወም እንዲለቀቅ ጠይቋል፡፡የእንግሊዝ መንግስት ግን ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግስት አጋርና አንዳርጋቸው ዜጋው ቢሆኑም በቤተሰቦቻቸው እንዲጎበኙና መደበኛ የሆነ ክስ እንዲመሰረትባቸው አልጠየቀም፡፡ባሳለፍነው ሳምንት የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ግራንት ሻፕስ የኢትዮጵያ መንግስት አቻቸውንና ሌሎች ባለስልጣናት ወደ ለንደን በመጋበዝ የንግድ ልውውጥ ስለሚደረግበት ሁኔታ መክረዋል፡፡
በሁለትዮሽ ግኑኝነቱ ወቅት ሻፕስ መንግስታቸው ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነቱ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዋና ጸሐፊ ፊሊፕ ሃሞንድ ከዝግጅቱ መጠናቀቅ በኋላ ለኢትዮጵያ ባለስልጣናት የአንዳርጋቸውን ጉዳይ እንዳነሱባቸው ቢናገሩም ከእስር እንዲፈቷቸው ግን አልጠየቁም፡፡
በሪፕራይቭ የሞት ቅጣት ተከራካሪ ቡድን አባል የሆኑት ማያ ፎ ‹‹አንዳርጋቸው የሶስት ልጆች አባትና እንግሊዛዊ ነው፡፡ለ16 ወራት ያህል በኢትዮጵያ ባለስልጣናት ለእስር ተዳርጎ ቶርቸር ተፈጽሞበታል፡፡በሌለበትም ሞት ተላልፎበታል፡፡ወደ እንግሊዝ የሚመለስበት ብቸኛው መንገድ ስርዓተ ቀብሩ ሲፈጸም እንደሆነ እንደሚሰማው መናገሩ በጣም አስደንጋጭ ነው፡፡አንዳርጋቸው ከህገ ወጥ እስሩ እንዲለቀቅ ከመጠየቅ ይልቅ የእንግሊዝ ሚኒስትሮች ልዩ የንግድ ትርኢት ባሳለፍነው ሳምንት ማዘጋጀታቸው አስገራሚ ነው፡፡ግዜው ሳይዘገይ የእንግሊዝ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንዳርጋቸው እንዲለቀቅና በለንደን የሚገኙትን ቤተሰቦቻቸውን እንዲቀላቀሉ በአስቸኳይ መጠየቅና መጫን ይኖርባቸዋል››ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
የኢህአዴጉ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም አንዳርጋቸው የአዳማውን አዲስ የፍጥነት መንገድ መጎብኘታቸውንና ላፕ ቶፕ ተሰጥቷቸው መጽሐፍ እየጻፉ እንደሚገኙ ለቪኦኤ በሰጡት አስገራሚ ቃለ ምልልስ መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/47735#sthash.9ZeogJna.dpuf