Friday, April 22, 2016

ስደት፣ መከራ፣ እስራት፤ ለምን

ሰዎች  በተለያየ  መልኩ  ሀሳባቸውን  ሲገልጹ  በማሰተዋል  እና  በትኩረት  እንመለከታቸዋለን  የሁላችንም  ሀሳብ እንዳመለካከታችን  ብሎም  እንደአሰተሳሰባችን  እኛ  በገመትነው  ሁኔታ  ለመግለጽ  እና  ለማሰረዳት  እንሞክራለን  ነገሮችን በቅንነት  ወይም  በመልካም  ጎን  ማንፀባረቅ  ማሳየት  የምንችልበት  ሁኔታዎች  ማዳበር  በሰዎች  ህሊናውስጥ  እንዲሰርፁ  እኛ ምሳሌዎች  ሆነን  መቅረብ  አለብን

በመንፈሳዊ  ህይወትም  እንዲይላል  የእግዚአብሔር  መንፈስ  አንድ ነው  ፀጋ  ግን  የተለያየ  ነው  ይህም  ማለት  ለምሳሌ የመስበክ  ወይም  የማስተማር  ፣የመዘመር  ሌሎችም  የመሳሰሉት  እንደተሰጠው  ፀጋ  በመንፈሳዊ  ህይወት  ያገለግላል  ማለት ነው  ወደ  ፖለቲካው  ስንመጣ  የስነፁሁፍ  ችሎታ   ያለው  በመጻፍ ፣ ህዝብን  ለለውጥ  የሚያስተባብር  የሚቀሰቅስ የሚያደራጅ  በማደራጀት  ፣ በፋይናንስ  ወይም  የኢኮኖሚ  ድጋፍ  የሚያደርግ  በሀብቱ ፣ ከተለያዩ  ሚዲያዎች  ወይም የዜና ጣቢያዎች  የሚያገኛቸውን  ኢንፎርሜሽኖችን  የሚያሰራጭ  ሁሉም  እንደችሎታውና  እንደአቅሙ  እንደፍላጎቱ  የበኩሉን አስተዋጾ  ካደረገ  አንደኛው  ካንደኛው  የሚያንስበት  እና  የሚበልጥበት  ሁኔታ  የለም  ሁሉም  እንደመልካም  አስተሳሰቡ  ነው
ሁሌም   በመልካም   ስራቸው   የምንወዳቸው   የምናከብራቸው   የትግል   አርያነታቻውን   የምንከተላቸው  የሚያስተምሩን  በርካታ   ኢትዮጵያኖች  ሰፊውን   ግዜያቸውን   እውቀታቸውን፣  ህይወታቸውን ፣  ገንዘባቸውን ፣   በየእስርቤቱ   ያለአግባብ  የሚሰቃዩ   ስለህዝቦች   ነጻነት ሲሉ  መሰዋትነት  የሚከፍሉ  ብዙ  ኢትዮጵያኖች   አሉን  ዘወትር   የወያኔን  ዘረኛ  መንግስት በምንመልኩ  እናስወግድ  በሚለው  ላይ ነው  ትኩረታቸዉ   እንጅ ስለግለሰቦች  ወቀሳ ማቅረብ  አይደለም፣፣  በሌላምመልኩ ደግሞ   አንዳንድ  ግለሰቦ ች ከእኛ  ዉጭ  ኢትዮጵያዊነት ፣አዋቂ   ለአሳር  ነዉ፣  እን ዲያዉም   ከኛ  ዉጭ  ፉጬት  አፍ ሟሞጥሞጥ ነዉ፣  የሚሉ አካላት  አሉ፣፣   ምናልባት   ከዉስጥያለ   ኢትዮ ጵያዊነት፣ ወይም   ለወገን   ተቆርቋሪነት  ሊሆን ይችላል፣፣  ይህ  ስሜት   በሁላችንም   ወስጥያለ  ነገር   ቢሆ ንም  የሚንገልጽበት   መንገድ ሊለላይ ይችላል፣፣ አንዳንድ ሰዎ ች አቅማቸዉንና   እዉቀታቸዉ  በሚፈቅደዉ  ደረጃ የሚያደርጉትን  መልካም  ስራ  በሰዎች  ዘንድ  ለታይታ   ወይም  እዉቅና   ለማግኘት   ብቻ   ሳይሆን   በመጀመርያ   ደረጃ  እንደሰብዓዊ   ፍጡር   ማለትም   እንደ   ሰዉ   ከዛም   ቀጥሎ  እንደ ኢትዮጳያዊነት   ለሃገር እና  ለወገነ   ምን  ማድረግይገባኛል   ብለዉ   በሚኖርበትሃገር   ወይንም   አከባቢ  ያለዉን  የወያኔን የግፍ  አገዛዝ  በመቃዎምና  በማውገዝ   እንደሁም   የትግሉ   ተካፋይ   በመሆን፣   ኢትዮጵያ   የሁሉም   ብሄርና   ብሄረሰቦች ሃገር   መሃኑዋን   በተቃራኒወ  ደግሞ   የአንድ  ብሄርየበላይነት  የሚንጸባረቅበት  በሁሉም  መስክ  ማለትም  በኢኮ ኖሚ ፖሊቲካና   ወታደሪዊ  ሃይላት ሁሉንም  ተቆ  ጣትረዉ እንደያዙት፣፣

ለኢትዮጵያ      ያሰብነዉን   የነጻነት፣  የፍጥ ፣ የዲሞ ክራሲ እና   የእኩልነት  ሃገር  መገንባት  የሚንችለዉ፣፣  የተወሰኑ ሰዎች   መስዋእትነት   እየከፈሉ፣  የእነሱን ችግር   በማራገብ  ብቻ  የሚገኝ  ነጻነት  የለም፣፣  እያንዳንዱ  በያለበት  ቦታ በሃሳብ፣  በቁሳቁስ  ወይንም  በገንዘብ  ድጋፍ  የትግል  አጋርነቱን  መግለጽ  አለበት፣፣ሁልግዜ  ሰዎችን  ስንወቅስ  ስንኮንን  እንታያለን  በርግጥም  የሚወቀሰው  በአግባቡ  መወቀስ  አለበት  ሁላችንም  አመልካች ጣታችን  ወደ  ሰዎች  ስንቀስር  ሶስቱ  ጣታችን  ወደራሳችን  መሆኑን  አናስተውልም  ይህን  ለማለት  ያነሳሳኝ  አብይ  ነጥብ የራስን  ምሶሶ  የሚያክል  ጉድፍን  በአይናችን  ውስጥ  እያለ የወንድማችን  ወይም  የእህታችን  ስንጥር  የሚያክል  ጉድፍን መመልከት  እንወዳለን  እከሌ፨ሊት  ምንሰራ፨ች  ወይም  ምንድነው፨ናት  ከማለት  የልቅ  እኔ ምንሰራው  እኔ  ማነኝ  ብሎ  እራስን  መጠየቅ  አስተዋይነት   ነው።

No comments: