Saturday, October 19, 2013

ኢትዮጵያ እና የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ

ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ጣቢያ ሶስት የተለመዱ ስፍራዎች አሉ።አንደኛው ሰዎች ያለመብራት የሚታሰሩበት እና ጭለማ ቤት የሚባለው ነው።ሁለተኛው ለግርፋት የተመቻቸው ጣውላ ቤት የሚባለው ሲሆን ሶስተኛው ደግሞ በተሻለ ደረጃ የሚታሰሩበት እና ከዚሁ የተነሳ በሌስሊ ኣባባል «ሸራተን» ተብሎ የሚታወቀው ነው።
Thousands of Ethiopian opposition activists demonstrate in Addis Ababa on June 2, 2013. The protests were the largest in the country since post-election violence in 2005, in which 200 people were killed and hundreds more arrested. The activists have vowed to press ahead with demonstrations calling for government reforms and the release of political prisoners. The demonstrations were organised by the newly-formed Blue Party opposition group. Government spokesman Bereket Simon said up to 4,000 people joined Sunday's demonstration, while some observers put the number at 10,000. AFP PHOTO/STRINGER (Photo credit should read STRINGER/AFP/Getty Images)
የኢትዮጵያ ባለስልጣናት እስረኞችን ይገርፋሉ፥ ይደበድባሉ በተለያየ መንገድ እያሰቃያሉ በማለት ዓለም አቀፉ የመብት ተሟጋች ድርጅት ሒዩማን ራይትስ ዎች አጋለጠ።ሑዩማን ራትስ ዋች ዛሬ ባወጣዉ ዘገባዉ እንዳስታወቀዉ የኢትዮጵያ ፀጥታ አስከባሪዎች በተለይ አዲስ አበባ ዉስጥ ማዕከላዊ ተብሎ በሚጠራዉ የፌደራሉ የምርመራ ማዕከል በፖለቲካ እስረኞች ላይ የሚደርጉት የምርመራ ዓይነትና ሒደት ሕገ ወጥ ብቻም ሳይሆን ሰብዓዊነትም የጎደለው ነው።የኢትዮጵያ ባለስልጣናት አፋጣኝ የማስተካከያ እርምጃ ይወስዱ ዘንድም ሂዩማን ራይትስ ዎች አሳስበዋል።የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ግን የሑዩማን ራይትስ ዋችን ወቀሳና ጥያቄ አጣጥለዉታል።ጅዓፈር ዓሊ ሁለቱንም ወገኖች አነጋግሮ ያጠናቀረዉ ዘገባ አለን።
በዚሁ ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ እስር ቤት የሚታሰሩት እና የሚመረመሩት ደግሞ በሪፖርቱ መሰረት የተቃዋሚ ፓርቲዎች መሪዎች አባላት እና ደጋፌዎችን ጨምሮ ጋዜጠኞች የተቃውሞ ሰልፍ ኣደራጆች እንዲሁም የእምነት እና የብሄር ተቐማት ደጋፌዎችም ጭምር ናቸው።
0,,16530143_404,00
በማዕከላዊ እስር ቤት የሚታየው የእስረኞች እያያዝም ሆነ የምርመራው ስልት በተለይም እ ጎ አ ከ 2010 ዓ ም ወዲህ እጅግ እየከፋ መምጣቱን የጠቀሰው የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ በእስር ቤቱ ውስጥ ሲገረፉ የነበሩ 35 የቀድሞ እስረኞችን እና ቤተሰቦቻቸውን ዋቢ በማድረግ ይህ ሁሉ የሚካሄደው እስረኞችን አስፈራርቶ አሰቃይቶ እና አደናግሮ መረጃ ለማወጣጣት ወይንም የሐሰት ሰነድ ለማስፈረም መሆኑን አውስቷል።
«ከተጭበረበረው» የ2005ቱ ምርጫ ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን ሁሉ በማዳፈን ላይ መሆኑንም ሪፖርቱ ያትታል።
አንዳንድ የቀድሞ እስረኞች ይላል ሪፖርቱ በጥፊ በእርግጫ በዱላ በጠመንጃ ሰደፍ እና በተለያዩ ነገሮች መደብደባቸውን ተነጥለው መታሰራቸውን እና ተዘቅዝቀው ከጣሪያ ወደታች መሰቀላቸውን ለሂማን ራይትስ ዎች አስረድተዋል።አንድ ከኦሮሚያ አካባቢ የተያዘ የኦሮሞ ተማሪም በማዕከላዊ እስር ቤት ለወራት በእግር ብረት እና በእጅ ካቴና መታሰሩን እና ከምግብ ጀምሮ ለመጸዳዳት ጭምር በእስረኞች እርዳታ ብቻ መክረሙን በምሬት ያስታውሳል ሲል ሂዩማን ራይትስ ዎች አስታውቀዋል።
0,,16358522_404,00
በሂዩማን ራይትስ ዎች የአፍሪካ ጉዳዮች ም/ዳይሬክተር የሆኑት ሚስ ሌስሊ ሌፍኮቭ እንደሚሉት በዚህ ማዕከላዊ ተብሎ በሚታወቀው የፌደራሉ የምርመራ ጣቢያ ሶስት የተለመዱ ስፍራዎች ኣሉ። አንደኛው ሰዎች ያለመብራት የሚታሰሩበት እና ጭለማ ቤት የሚባለው ነው። ሁለተኛው ለግርፋት የተመቻቸው እና ጣውላ ቤት የሚባለው ሲሆን ሶስተኛው ደግሞ በተሻለ ደረጃ እስረኞች እየተንቀሳቀሱ በጋራ የሚታሰሩበት እና ከዚሁ የተነሳ በሌስሊ ኣባባል «ሸራተን» ተብሎ የሚታወቀው ነው።
ከዚህም ሌላ ይላሉ ሌስሊ በማዕከላዊ እስር ቤት በእሳቸው ኣባባል ማጎሪያ ቤት እስረኞች ከዘመዶቻቸው እና ከህግ አማካሪዎቻቸው ጋር እንዳይገናኙ የሚደረግበት ሁኔታም ኣለ ከእትዮጵያ መንግስት በኩል የጠ/ሚ/ሩ ቃል ኣቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ ግን ይህ ከእውነት የራቀ እና የተለመደ የሂዩማን ራይትስ ዎች ተራ ድራማ ነው ይላሉ።የጸረ ሽብር ህግ ተብሎ የሚታወቀው የኢትዮጵያ ህግም መንግስት ተቃዋሚዎችን የሚያፍንበት ሰላማዊ እንቅስቃሴን የሚያሽመደምድበት እና በኣጠቃላይ ሰብዓዊ መብትን ለመጣስ የሚጠቀምበት ተጨማሪ መሳሪያ ነው ሲል የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ ይተቻል።
ጅዓፈር ዓሊ
አርያም ተክሌ

No comments: