Sunday, September 28, 2014

በቦስተን የ2007 ዓ. ም. የደመራ በዓል በሺህ የሚቆጠሩ የቦስተን እና አካባቢዋ ነዋሪዎች በተገኙበት በድምቀት ተከበረ- አቡጊዳ


ቦስተን መስከረም 17/2007 (ሴፕቴምበር 27፣ 2014 ዓ.ም) የደመራ በዓል በካምብሪድጅ ከተማ 808 Memorial Dr. አጠገብ በሚገኘው ፓርክ በቦስተን እና አካባቢዋ ነዋሪ በሆኑ የመካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካዔል ቤተ ክርስቲያን እና የመካነ ሰላም ቅዱስ ሚካዔል ቤተ ክርስቲያን እና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕምናን ዘንድ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ተከበረ።
በበዓሉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን የመካነ ሕይወት ቅዱስ ሚካዔል ቤተ ክርስቲያን እና የመካነ ሰላም ቅዱስ ሚካዔል ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን አባቶች፤ ዲያቆናት እና መዘምራን በቦታው በመገኘት በዓሉን በታላቅ መንፈሳዊ ስነ ስርዓት አክብረዋል።
በየዓመቱ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የመስቀል በዓል ላይ የቤተ ክርስቲያኖቹ አባቶች ስለ በዓሉ ታላቅነት እና የበዓሉን ታሪካዊ እና ሐይማኖታዊ አመጣጥ በተመለከተ ሰፋ ያለ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን፤ መዘምራኖችም በዓሉን የተመለከቱ መንፈሳዊ መዝሙሮችን በመዘመር ለበዓሉ ትልቅ ድምቀት ሰጥተውታል።
የቦስተን እና አካባቢዋ ምዕመናን በዓሉን አስመልክቶ የጧፍ ማብራት ስነ ስርዓት በማድረግ እና መንፈሳዊ ዜማዎችን ከመዘምራን ጋር በማዜም ተጠናቋል። (ፎቶግራፎችን ይዘናል ይመልከቱ)
በዚሁ አጋጣሚ የአቡጊዳ ዝግጅት ከፍልም ለመላው የቦስተን እና አካባቢዋ ኢትዮጵያውያን ነዋሪዎ፤ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች “እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደርሳችሁ” እያለ መልካም ምኞቱን እየገለጸ፤ ባለፈው ዓመት የመስቀል በዓል በተባበሩት መንግስታት የሳይንስ፣ ባህልና ትምህርት ድርጅት /ዩኔስኮ/ መመዝገቡንም በዚሁ አጋጣሚ ለማስታወስ እንወዳለን።10338915_859925697364934_1208190373_n - Copy
10370561_859925527364951_714344135_n
unnamed
10708236_859925820698255_317399740_n - Copy
10708236_859925820698255_317399740_n
10708277_859925717364932_1270797296_n
10711699_859925544031616_1571072479_n
10714813_859925744031596_68679264_n
10715967_859925674031603_1988561230_n - Copy
10719495_859925800698257_1925251979_n - Copy

No comments: