Friday, October 24, 2014

ከ50 በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ደቡብ አፍሪካ ሊጓዙ ሲሉ መያዛቸውን የኬንያ ፖሊስ አስታወቀ


ጥቅምት ፲፫(አስራ ሦስትቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያውያኑ በህገወጥ መንገድ መግባታቸውን የገለጸው የኬንያ ፖሊስ፣  54ቱ ኢትዮጵያውያን በአንድ ቤት ውስጥ ታጭቀው ተገኝተዋል ብሎአል።
ሰዎቹን ወደ ኬንያ ያመታው ግለሰብ መጥፋቱንም ፖሊስ ገልጿል። ኢትዮጵያውያንን ወደ ደቡብ አፍሪካ ማሻገር ትልቁ የገቢ ምንጭ እየሆነ መምጣቱን ፖሊስ ገልጿል።
ወደ ደቡብ አፍሪካ እንጓዛለን በማለት ሙከራ ያደረጉ ኢትዮጵያውያን፣ በ ዝምባብዌ፣ ታንዛኒያ፣ ኬንያና በሌሎችም አገራት ታስረው እንደሚገኙ ዘገባዎች ያመለክታሉ።  sourse esat

No comments: