Saturday, October 25, 2014

ወያኔ በወገኖቻቸን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና መከራ በቃ ማለት የገባናል

ወያኔ የጥቂት ባለሃብቶችን እና የታማኝ ካድሬዎችን ጥቅም ብቻ ለማስከበር ብሎም የስልጣን ጥማቸውን ላይ ቆይታቸውን ለማርዘም የኢትዮዽያ ህዝቦች  በሚያነሱት የነፃነት ጥያቄ በወያኔ እስር ቤት በግፍ የታጎሩ የነፃነት ናፋቂዋች ልጆች ቁጥራቸው እጅግ ከፍተኛ ነው – በብዙ ሺዎች እንደሚቆጠር ይታወቃል። በየቦታው ባሉ የወያኔ እስር ቤቶች ታጉረው የሚገኙ ጋዜጦኞች እና የዞን፱ ብሎገሮች ፣ የድምፃችን የሰማ
ኮሚቴዎች የተለያዩ እስረኞች ቤት ይቁጠረው ።
በተለያዩ ግዚያቶች ኢትዮጵያ ውስጥ የሚደርሱትን የመብት እርገጣ የጋዜጠኞች መሰደድ የመፃፍና ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ
መብት እንዴሊለ ብዙ ጥናት ያደረጉ የአለማቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች አመላክተዋል።  በዚህ ወቅት ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር አለን ብለው በውሸትየአለምን ህዝብ   ለማታለል መሞከር ገዢው ወያኔ በፍፁም ዲሞክራሲን በስም እንጂ በተግባር የማያውቅ መሆኑን ለተመለከተው ሰው ሁሉ ግልፅ ነው። በየትኛው በመከፋፈል   በግፍ የሚገዛው የኢትዮዽያ ህዝብ ያለውን ንቀት ያሳያል።

አምባገነኑ የወያኔ ስርአት ርህራሄ ከሌለው እስራቱም አልፎ  የኢትዮጵያን  ህዝብ እያደነ ይገኛል ጨካኙ የወያኔ መንግስት በኛ  ዘንድ እያደረሰ ያለውን ግድያ፤ እስርና ማሰደድ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ወያኔ ካድሬዎቹን ተጠቅሞ  ህዝብ ላይ የሚያደርገውን ኢሰብአዊ ድርጊት ኢትዮጵያውያን   ተሰደው በሚኖሩበት የጎረቤት አገሮች ጭምር ደርሷል፡፡  ኢትዮጵያውያን  ከጎረቤት አገሮች አሳፍኖ በመውሰድ የተቃዋሜ ደጋፊዎች ናችሁ እያለ የሚፈፅመውን ግድያ እና እስራትም እጅግ ከፍቷል፡፡ በመቃወም  ላይ የወያኔ መንግስት የግድያ ማስጠንቀቂያ ከመስጠት ጀምሮ አስከፊ ድርጊቱን በእስር ቤት እየፈፀመባቸው ይገኛል፡፡ ስለዚህ የወያኔ መንግስት እየፈፀመ ያለውን ግድያ፣ እስራት፣ ከትምህርት ገበታ ማፈናቀል እና ኢፍትሀዊ ውሳኔውን ለመጋፈጥና ነፃነቱን ለማወጅ  ህዝብ በጋራ መነሳት ያለበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ የወያኔ መንግስት ከመቼውም ጊዜ የከፋ ጫና በጋዚጠኞች ብሉገሮች  ላይ እያደረሰ   የተለያዩ ተቀጽላ ስሞችን እየሰጠ ሊደርስበት ከሚችለው የዘር ማጥፋት ውንጀል ለመሸሽ ሲውተረተር አይተናል ህዝብ ነፃነት መጎናፀፊያው ወቅት እየቀረበ መሆኑን የሚያሳይ በመሆኑ የኢትዮጵያን ህዝብ  ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ሁኔታ እጅ ለእጅ ተያይዞ መብቱን መጠየቅ አለበት፡፡

በመጨረሻም ያለምንም ወገናዊ እና ሰብአዊ ስሜት ህዝባችንን እየገደለ፤ እያሰረና እያሰደደ እንዲሁም ታሪካችንን፤ ባህላዊ እሴታችንን እና ሃይማኖታችንን ጭምር ጥላሸት እየቀባ፤ የተፈጥሮ ሃብታችንን በመመዝበር ለግል ጥቅም እያዋለ ያለውን አምባገነኑን የወያኔ መንግስት ማስወገድ የምንችለው እራሳችንን አደራጅተን በቆራጥነት ተነስተን በጋራ እርምጃዎችን መውሰድ ስንጀምር ነው። ስለዚህ እኛ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ነገ ሳንል በጋራ ዝምታዉ ይሰበር በማለት ለነፃነት እጅ ለእጅ ተያይዘን ወያኔ እስከ አፍንጫው የታጠቀውን ትጥቅ በማስፈታት ህዝባችን የወየኔ ከፉፍለህ ግዛ የሚለዉን የህዝብ መጨቐኛ መንገድ ልናወግዝ ይገባል። ፍርሃት በቃ ብለን ልንነሳ የሚገባበት ሰአት አሁን ነው። ከፍርሃት ቆፈን የተላቀቀ ህዝብ ደግሞ መሳሪያ ሳይገታው እራሱን በማደራጀት ነፃነቱን ለማወጅ ጊዜ አይወስድበትም። ወገኔ የኢትዮጵያውያን ህዝብ ሆይ ህዝባችን ከታሠረበት የመከራ ሰንሠለት በጣጥሰን ለማውጣት ያሉንን አማራጮች ሁሉ አሟጠን መጠቀም እንዳለብንም መዘንጋት የለበትም። በተለይ ጠላታችን የሆነውን የወያኔ መንግስት በትግል ገርስሶ ለመጣል ነጻነት ብለዉ በመናገር መታገል ድል ለህዝቦች ሞት ለወያኔ በማለት ጐን ለጞን በመሰለፍ መነሳት ይኖርብናል።

ድል ለሰፊው ኢትዮጵያውያን ህዝብ                                                                                                                                                                                                     ፍቅርተ ነጋሳ

No comments: