Thursday, April 17, 2014

ሚሊዮኖች ድምጽ – የእሪታ ቀን ሰልፍ በሚያዚያ 26 ቀን እንደሚደረግ የአዲስ አበባ አስተዳደሩ እውቅና ሰጠ !


by admin
«ህግንአክብረንለድርድርየማናቀርበውንህገመንግስታዊመብታችንንአሳልፈንአንሰጥም።ታላቁህዝባዊሰላማዊሰልፍ ‹‹የእሪታቀን ›› በሚልመሪቃልሚያዚያ 26፣2006 ዓ.ምበአዲስአበባከተማይደረጋል፡፡» ሲሉ የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌው ገለጹ።
ፓርቲዉ ከአዲስ አበባ አስተዳደር አስፈላጊዉን እውቅና ያገኘ ሲሆን ፣ ከትንሳኤ በዓል በኋላ በሃያ ሶስቱም የአዲስ አበባ ወረዳዎችና በአዲስ አበባ አካባቢ ባሉ ቦታዎች ቅስቀሳ እንደሚያደርግ ለማወቅ ተችሏል። የአዲስ አበባ ሕዝብ በዚህ ቀን፣ በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ያሰማል ተብሎ ይጠበቃል።
ሰልፉ ሊደረግ የታሰበው መጋቢት 28 የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ አስተዳደሩ ሕግን ባልጠበቀ መልኩ፣ አማራጭ ቀን ወይም ቦታ እንዲቀርብ ሳይጠይቅ በደፈናዉ እውቅና አልሰጠም የሚል ደብዳቤ መላኩ ይታወቃል። ለሕገ ወጥ እርምጃ እውቅና አንሰጥም በሚል፣ አንድነት የአስተዳደሩን ደብዳቤ እንደማይቀበል በማሳወቅ፣ የቅስቀሳ ዘመቻ ማድረጉን ፣ ከዚያም ጋር በተገናኘ 4 አባላት በፖሊስ መደብደባቸውን ፣ አምስት ደግሞ ለሳምንት መታሰራቸው ይታወቃል።
አስተዳደሩ የላከዉን ሕገ ወጥ ደብዳቤ በመቀልበስ፣ ለሚያዚያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም  በአዲስ አበባ ከተማ ሰልፍ እንዲደረግ እውቅና  እንዲሰጥ መደረጉ ፣ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ያደረጉት ትግል ዉጤት እንደሆነም የሚያመላክት ነው።



Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments: