Wednesday, April 30, 2014

የቀድሞው የአረና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃምን ጨምሮ ታዋቂ ፖለቲከኞችና ምሁራን አንድነት ፓርቲን ተቀላቀሉ -ፍኖተ ነፃነት

mnhe abugda


የቀድሞው የአረና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃምን ጨምሮ ታዋቂ ፖለቲከኞችና ምሁራን አንድነት ፓርቲን መቀላቀላቸውን አንድ አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡
ከፍተኛ አመራሩ ለፍኖተ ነፃነት እንደገለፁት ታዋቂው ወጣት ፖለቲከኛና ደራሲ አቶ አስራት አብርሃ እና ሌሎች በርካታ ወጣት ምሁራን አንድነት ፓርቲን መቀላቀላቸው ፓርቲው በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል እያገኘ ያለውን ተቀባይነት የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ አቶ አስራት አብርሃም በቅርቡ በአንድነት ፓርቲን መቀላቀላቸውን በልዩ መርሀግብር ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ በሂደት አንድነትን እየተቀላቀሉ ያሉ የሌሎች ታዋቂ ፖለቲከኞችና ምሁራን ስም ይፋ እንደሚደረግም ከፍተኛ አመራሩ ለፍኖተ ነፃነት ተናግረዋል፡፡
አቶ አስራት አብርሃም “ከሀገር በስተጀርባ”፣ “መለስና ግብፅ” ፣ “ፍኖተ ቃዬል” የሚሉና ሌሎች መጽሓፍትን የጻፉ መሆናቸው ይታወቃል፡10301125_850021588347637_5249739579259806473_n

No comments: