Thursday, April 24, 2014

የቢዚ ሲግናል፣ የጃሉድና የናቲ ማን የአዲስ አበባው ኮንሰርት ተዘረዘ


by admin
(ዘ-ሐበሻ) የታዋቂው የሬጌ ሙዚቃ ተጫዋች ቢዚ ሲግናልን አጅበው ኢትዮጵያዊያኑ ጃሉድ እና ናቲ ማን ይሳተፉበታል የተባለው የአዲስ አበባው ኮንሰርት ተሠረዘ። የፊታችን ቅዳሜ ቴዲ አፍሮ በግዮን ሆቴል ለዳግማዊ ትንሣኤ በዓል በሚያቀርበው ኮንሰርት ቀን በተመሳሳይ በሚሊኒየም አዳራሽ ይደረጋል ተብሎ የነበረው የነዚሁ ታዋቂ አርቲስቶች ኮንሰርት መሰረዝ የከተማው አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኗል።
የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኙ ቢዚ ሲንግናል

የአዲስ አበባ የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንዳስታወቁት ቢዚ ሲግናልን ጨምሮ በርከት ያሉ የሬጌ ሙዚቃ ተጫዋቾጮች በተለይም ጸረ ግብረሰዶማዊ አቋም ስላላቸው በአብዛኛው በግል አውሮፕላኖች እንደሚጓዙ ጠቅሰው ወደ አዲስ አበባም በግል አውሮፕላን ለመሄድ አስበው አውሮፕላን አለመገኘቱን ጠቅሰው ለኮንሰርቱ መሠረዝም ምክንያት ሊሆን ይችላል የሚሉ ወገኖች እንዳሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት የጸረ ጌይ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ፈቃድ ሰጥቶ እያለ በኋላም ሰልፉ እንዲቀር ከተደረገ በኋላ የጸረ ጌይ አቋም ያለው ድምጻዊ ቢዚ ሲግናል ኮንሰርት መሰረዙ ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል።

በሚሊኒየም አዳራሽ ለዳግማዊ ትንሳኤ የፊታችን እሁድ ይደረጋል ተብሎ የነበረው ኮንሰርት ከተሰረዘ በሁላ የተሰጠው ምክንያት ለዘፋኙና ባንዱ ማመላለሻ የአውሮፕላን ማጣት ይሁን እንጂ ከበስተጀርባው የጸረ ጌይ ጉዳይና ሌሎችም ነገሮች ሊኖሩ እንደሚችሉ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ። በሌላ በኩል ቴዲ አፍሮ የፊታችን ቅዳሜ ምሽት በጊዮን ሆቴል ለሚያደርገው ኮንሰርት በትናንትናው ዕለት የመድረክ ግንባታ ሥራ መጀምሩን ለማወቅ ችለናል።
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments: