Saturday, May 31, 2014

በሊቢያ በርካታ አስከሬኖች ተገኙ

 | 


ኢሳት ዜና :-ከሳምንታት በፊት በርካታ ስደተኞችን ጭና ከሊቢያ ወደ ጣሊያን ስታምራ በሰጠመችው ጀልባ ተሳፍረው የነበሩ ሰዎች ሳይሆን እንዳልቀረ የተገመተ አስከሬን መገኘቱን የሊቢያ የአደጋ መከላከ ሰራተኞችን በመጥቀስ ዓለማቀፍ ሚዲያዎች እየዘገቡ ነው።
የሊቢያ አደጋ መከላከል ሰራተኞች በጀልባዋ ከ150 በላይ ስደተኞች ተሳፍረው እንደነበር ለ አል ጀዚራ የገለጹ ሲሆን፤ እስካሁን የተገኘው ግን የ 20 ዎቹ አስከሬን
አበዛኞቹ ተሳፋሪዎች ከአፍሪካ የመጡ እና በሊቢያ በኩል ወደ ጣሊያን ለመሻገር የሞከሩ ስደተኞች እንደሆኑ ተመልክቷል።
እስካሁን 20 አሰከሬኖችን ከባህር ውሰጥ ያወጡት የሊቢያ አሰከሬን ፈላጊዎች፤ ቀሪዎቹን ወደ 130 የሚገመቱ ተሳፋሪዎች አስከሬን ለማውጣት እርዳታ ይደረግላቸው ዘንድ ጠይቀዋል።
ቢቢሲ ከዚሁ ጋር ተያይዞ እንደዘገበው በዚህ ዓመት ከመላው ዓለም ወደ አውሮፓ የሚሻገሩ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ እና በአስደንጋጭ ደረጃ ጨምሩዋል።
ካላፈው የፈረንጆች ዓመት መግቢያ እስከ አፐሪል ድረስ ባሉት አራት ወራት ብቻ 42 ሺህ ስደተኞች በህገ ወጥ መንገድ ወደ አውሮፓ መሻገራቸውን ያመለከተው ቢቢሲ፣ከነኚህ መካከል 25 ሺ 650 የሚሆኑት በሊቢያ ድንበር አድርገው ወደ ጣሊያን የገቡ መሆናቸውን ጠቀሱዋል።
በተለይ በሰሜን አፍሪካና በአረቡ ዓለም የተቀጣጠሉት አብዮቶች ለስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመር ዋነኞቹ ምክንያቶች እንደሆኑ ተጠቅሱዋል።

ethsat radio
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments: