Thursday, May 15, 2014

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ካፒቴን አስመራ ላይ ተቃዋሚዎችን ተቀላቀለ፤ * መንግስት አላስተባበለም

 | 


(ሚግ 23 - ፎቶ ከፋይል)
(ሚግ 23 – ፎቶ ከፋይል)

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ አየር ሃይል አባላት ገዢውን የኢሕአዴግን መንግስት በመክዳት ወደ ተለያዩ ሃገራት የሚያደርጉትን ስደት ቀጥለዋል። የኤርትራ ሚዲያዎች የመንግስታቸውን ቃል አቀባይ በመጥቀስ እንዳስነበቡት ሰሞኑን የኢትዮጵያ ሚግ 23 አብራሪ የሆነው ካፒቴን ዳንኤል የሽዋስ ስርዓቱን ጥሎ አስመራ ገብቷል።
እንደኤርትራ ሚዲያዎች ገለጻ ከሆነ ካፒቴን ዳንኤል የሺዋስ ኤርትራ ከሚገኙ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ተቀላቅለዋል። ሚዲያዎቹ በምን መልኩ ወደ አስመራ እንደገባ የገለጹት ነገር ባይኖርም ማዕዶት የተባለው የኤርትራውያን የመረጃ መረብ የኤርትራን መንግስት ቃል አቀባይ በመጥቀስ ካፒቴኑ ለኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት እጁን የሰጠው ከነ አውሮፕላኑ ነው ሲል ዘግቧል።
የኢሕአዴግ መንግስት በመከላከያ ውስጥ ያለውን የዘር አድልዎና በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በቸልታ መመልከት እያንገፈገፋቸው የሚገኙ የሠራዊቱ አባላት በተለያዩ ጊዜያት እየሸሹ ወደ ኤርትራ በመግባት ተቃዋሚዎችን እንደሚቀላቀሉ በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ መንግስት ካፒቴን ዳንኤል የሽዋስን መክዳት አስመልክቶ ምንም ያወጣው መግለጫ የለም። ዘ-ሐበሻ ከመንግስት አካባቢ ዜናውን ለማረጋገጥ ያደረገችው ጥረት አልተሳካም።
Ze-Habesha Website may contain advice, opinions, and statements of various information and content providers. The Website neither represents nor endorses the accuracy of information or endorses the contents provided by external sources. All blog posts and comments are the opinion of the authors.

No comments: