Friday, August 9, 2013

ሀገር ወዳድ መሆን እኮ ጦርነትን በሀገር ላይ ማሰብ አደለም፤ ሀገር ወዳድ እኮ መንግስት ህዝቡን ሲበድለው የራስን ኑሮ ደልቀቅ አድርጎ ማየት አደለም፤ ህዝብ ሲራብ ቆሞ ማየት አደለም፡፡ ምን አልባትም ችግርን አብሮ መጋፈጥ ትልቅ እሴት አለው


Thursday, August 8, 2013

የጀርመን ድምጽ ራዲዮ በቅጥረኞች የተሞላ የአምባገነኖች አለቅላቂ

በጥቅም የተገዙ እና የሙያ ስነምግባርን ያልተከተሉ ጋዜጠኞች አምባ
በምንሊክ ሳልሳዊ
"ከዽምጽ ጩኸት በስተቀርና ተደበደቡ ከሚባለው ውጭ ..የሰማነው ያየነው የለም"ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ የወያኔ አለቅላቂ

"የሙስሊሙ ወጣቶች በሰላም ወደ ቤት ሲመለሱ ነው ያየሁት ...ፖሊሶች መንገድ ዳር ከመፍሰሳቸው ውጪ ሲተናኮሉ አላየሁም....ደረሰ የተባለው ድብደባ እና እስር ሲባል ከመስማት ውጪ አላየሁም::..."ዮሐንስ ገብረእግዚአብሄር የሕወሓት አባልና የጀርመን ራዲዮ ዘጋቢ (እጅግ ዘረኛ)


የጀርመን ራዲዮ ጋዜጠኞች የወያኔን መውደቅ ተከሎ ከኢቲቭ እኩ ለፍርድ የሚቀርቡ መሆኑን ልንነግራቸው እንወዳልን::
በኢድ አልፈጥር በአል ወቅት በአዲስ አበባ መንግስት በሃይማኖታችን ጣልቃ አይግባ ጥያቄያችን ይመለስ ብለው በይፋ ተቃውሞ ያሰሙትን ሙስሊም ወገኖቻችንን የአምባገነኑ የወያኔው ፖሊሶች የጭካኔ ዱላቸውን ተጠቅመው ለሞት ለመቁሰል እና ለከባድ አደጋዎች ዳርገዋቸዋል ገለዋል ደብድበዋል አስረዋል አንገላተዋል::የጀርመን ድምጽ ጋዜጠኞች ሊያውቁት የሚገባ ጉዳይ ቢኖር የሙስሊሙ ጉድይ የእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ጉዳይ ነው ዘር ሃይማኖት እና ማንጛውንድ ደረጃ ሳይለይ የሙስሊሙ ጥያቄ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ነው:: እናንተ ብትዘባበቱበት እኛ ድፍን ኢትዮጵያውያን ግን የውስጣችን የደም ማንነታችን ያስተሳሰረን ስለሆነ አብረን በጋራ እንታገላለን እናሸንፋለን::

እውነታውን አለም አውቆት እየመሰከረ ባለበት ወቅት የአለም ሚዲያዎች ይህንንን እያስተጋቡበት ባለበት ጊዜ የቅጥረኞች ስብስብ የሆነው የጀርመን ድምጽ ራዲኦ ውሻ በበላበት ይጮሃል እንደሚባለው ጥያቄውን በአደርባይ የሆዳም ቋንቋ በመጠቀም ሊያልከሰክሰው ሞክሯል::ጌታቸው ተድላ ኃይለጊዮርጊስ ተብሎ ራሱን የሚጠራው ሆዳም አደርባይ ጋዜጠኛ ባቀረበው ዘገባ ላይ በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የተካሄደውን ጭፍጨፋ አቅልሎ በወያኔ የመጅሊስ ሹመኞች እና በካድሬዎቻቸው ቃለምልልስ ለመሸፈን ዳድቶታል:: የበላበትን የአምባገነኖች ወጪት ላለመስበር ኢሕኣዲጋዊ ሲቃ እየተናነቀው የዘገበው ጌታቸው ተብየው ሙስሊም ወገኖቻችን መደብደባቸው እና መታሰራቸው 'ደግ ኣደረገ መንግስት' በሚል ኢንተርቭው ዘግቶታል::/http://www.dw.de/popups/mediaplayer/contentId_17007641_mediaId_17008051

ከዚህ ቀደም ማንተጋፍቶት(ማሙሽ ስብሃቱ) የተባለ የዚሁ ራዲዮ የወያኔ አለቅላቂ  በፌስ ቡክ ባለፉት ሁለት አመታት የመጡ ኢትዮጵያውያን ጥያቄያቸው ፖስታቸው አግባብ አይደለም ያፈነገጠ ወዘተ በሚሉ ድፍን ሃሳቦች ሲወላገድ ነቅተንበት እጅ እና እግሩን እንዲሰበስብ አድርገነዋል የሱ ተከታይ የሆነው ሌላኛው የወያኔ አለቅላቂ በአረብ አገር ተደብቆ ሂጃብ የዘራፊ እና የዱርየ መከለያ ነው በማለት እንዲሁም ባለፉት አመታቶች አክራሪነት እየተስፋፋ ነው በሚል እደምታ የወገናችንን የሙስሊሙን ማንነት ከመዳፈርም አልፎ በትላንታው እለት የተደረገውም ተቃውሞ በሃገሪቱ ሙስሊሙ እየተደበደበ እየተገደለ እየታሰረ ባለበት ሰአት ይህ ግለሰብ በአረብ አገር ውስጥ ተደብቆ የፖሊስን ዱላ ወደ ጎን በመተው በድሬዳዋ እና በሌሎች...የኢድ ዝግጆቶች በሰላም ተጠናቀዋል በማለት የጻፈ ሲሆን የህዝብን የተቃውሞ ድምጽ ለመደበቅ ፈልጎ አልተሳካለትም::

በትላንትናው የኢድ በዓል በሺዎች ድምጻቸውን ያሰሙት በአንዋር እና በበኒን መስኪድ አይደለም ሙስሊሙ ህብረተሰብ የተመመው ወደ እስታዲየም ነበር ይህንን እያወቁ የጀርመን ጋዜጠኞች አንዋር እና በኒን መስኪድ ምን ሊያደርጉ ሄዱ? ሙስሊሙ የተደበደበው የታፈሰው የታሰረው በስታዲየም እና በአከባቢ እንጂ በሌላው መንገድ ላይ አልነበረም::እውን በአሉ የተከበረው ኢስታዲየም ነው ወይንስ በእነዚህ መስኪዶች ነው??ከዘገባዎቹ ብዙ ጥያቀዎች ማንሳት እንችላለን:: ሆዳሙ የሕወሓት አባል የሆነው ዮሃንስ ገብረእግዜር ተብሎ የሚጠራው ጋዜጠኛ ሙስሊሙ በሰላም ወደቤቱ ሲመለስ ተመልክቻለሁ በማለት ተራ የሆኑ ቃላቶችን ተጠቅሞ የፈሰሰውን ደም እንደውሃ ሊነግረን ፈልጓል::http://www.dw.de/popups/mediaplayer/contentId_17007641_mediaId_17008432 ይህ ዮሃንስ ተብሎ የሚጠራው የሕወሓት አባል በኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ዘንድ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰ እና ደረሰ የተባለውንም ከመስማት ውጪ እንዳላየ ዘግቧል::የጋዜጠኝነት ስራ ምን ያህል ድረስ ነው ብለን እንድንጠይቅ አድርጎናል::ፖሊሶች በየመንገዱ ዳር ከመፍሰሳቸው ውጪ ወንጀል ሲፈጽሙ እንዳላየ ተናግሯል:: ዮሃንስ የተባልከው ሆዳም ቅጥረኛ የተገደሉት የታሰሩት የተደበደቡት ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ደም ይፍረድብህ ወያኔ ነገ አፈር ይበላል ጀርመን ተደበቅ አሜሪካ ሁን ኢትዮጵያ ጆሮህን ይዘን ለፍርድ እናቀርብሃለን::ምንሊክ ሳልሳዊ

No comments: